ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው አረፉ!

Date:

የሮም ፓትርያርክና የካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪ የነበሩት ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ማረፋቸውን ቫቲካን በይፋ አስታውቋል።

ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በ2013 የቀድሞ ጳጳስ በነዲክቶስ 16ኛ ከሥልጣናቸው ከለቀቁ በኋላ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪ ሆነው ተሹመዋል።

የእርሳቸውን ማረፍ በተመለከተ ካርዲናል ኬቨን ፋረል በቫቲካን በኩል በላኩት የሐዘን መግለጫ ላይ “ውድ ወንድሞቼና እህቶቼ፣ በከባድ ሐዘን ቅዱስ አባታችን ፍራንሲስ ማረፋቸውን ላሳውቃችሁ እወዳለሁ” ብለዋል።

ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የካቶሊክ አማኞች ዘንድ ያላቸው ፍቅርና ተቀባይነት ከፍተኛ እንደነበር ይታወቃል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...