ሰላማዊ ሰልፉ ተካሄደ

Date:

ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ/ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ “አፈሳ ይቁም ሰላም ይስፈን” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል።

ይህ ሰላማዊ ሰልፍ በዋናነት በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ ቀውስ ለመቃወም፣ የአፈሳ ተግባራት እንዲቆሙ ለመጠየቅ እና ለፌደራል መንግስት እንዲሁም ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድምፅን ለማሰማት ታስቦ የተዘጋጀ ነው።

በዕለቱም ሰልፈኞቹ “የትግራይ እናቶች እንባ ይቁም” የሚሉና ልዩ ልዩ መልዕክቶችን ያዘሉ መፈክሮችን በማንገብ ድምፃቸውን አሰምተዋል።

ከማለዳው 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የተካሄደው ይህ ሰልፍ፣ በርካታ ቁጥር ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ሲሆን፣ መልእክታቸውን በሰላማዊ መንገድ ማስተላለፋቸው ተገልጿል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ...

ሱልጣን ቢን ኻሊፋ ግሩፕ በኢትዮጵያ በሆቴል ዘርፍ ሊሰማራ ነው

በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር...

የአሜሪካ የታክስ ህግ የስፔንን የዓለም ዋንጫ ሽልማት ስጋት ላይ ጣለ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ከዓለም ዋንጫ ሊያገኘው ከሚችለው 50 ሚሊዮን...

ህወሓት ከሌሎች ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር የሚደረግ ጥምረት አስፈላጊ መሆኑን ገለጸ

ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ...