በሚቀጥሉት አስር ቀናት አዲስ አበባን ጨምሮ በአብዛኛው የኢትዮጵያ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቴዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል ።
አሁን ያለንበትን የየካቲት ወር ጨምሮ እስከ ግንቦት ድረስ በሚዘልቀው የበልግ ወቅት፣ ሰሞኑን እየታየ ያለው የአየር ሁኔታ ለውጥ የሚጠበቅ መሆኑን በማስታወስ ፣ በተለይም የሀገሪቱ ደቡባዊ አጋማሽ ማለትም የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍል፣ የጉጂና ቦረና ዞኖች፣ የሲዳማ ክልል እንዲሁም የደቡብና ደቡብ ምዕራብ አካባቢዎች እስከ 55 በመቶ የሚሆነውን የዝናብ መጠን የሚያገኙበት ዋነኛ ወቅታቸው እንደሆነ ተጠቁሟል።
የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አሳምነው ተሾመ እንደተናገሩት ፣ የደቡብና ምስራቅ ትግራይ፣ የምስራቅ አማራ፣ የምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች፣ አዲስ አበባና የመካከለኛው ኢትዮጵያ ክፍሎች ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በመሆኑ ከቀላል እስከ ከባድ ዝናብ ይጠበቅባቸዋል።
የሚጠበቀው የዝናብ መጠን የእርሻ ስራዎችንና የአካባቢ ጥበቃ ተግባራትን ለመከወን እጅግ አመቺና ተስማሚ በመሆኑ ምንም ዓይነት ጉዳት እንደማያስከትል ታውቋል።
በሚቀጥሉት ቀናት የአየር ንብረት ለውጥ እንደሚኖር ተገለፀ
Date:
