በዛሬው ዕለት ከተደረጉ 13 የላብራቶሪ ምርመራዎች ተጨማሪ 2 ሰዎች ላይ የማርበርግ ቫይረስ መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
በዛሬው ዕለት በተደረገው ምርመራ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው ታማሚ ከዚህ በፊት ከተገለፀው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጂንካ ከተማ በለይቶ ማቆያ የነበሩ ሲሆኑ በተመሳሳይ ቦታም የህክምና ክትትላቸውን እያደረጉ እንደሚገኙ ሚኒስቴሩ ገልጿል።
በተጨማሪም በዛሬው ዕለት አንድ ሰው በቫይረሱ ህይወቱ ሲያልፍ በአጠቃላይ በቫይረሱ ህይወታቸው እንዳለፈ የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር አራት መድረሱ ተጠቁሟል።
በሽታው መከሰቱ ከተገለጸበት ቀን አንስቶ እስካሁን 46 የላብራቶሪ ምርመራዎች የተከናወኑ ሲሆን በአጠቃላይ ቫይረሱ በ8 ሰዎች ላይ መገኘቱ ተመላክቷል። እንዲሁም አራት ሰዎች ደግሞ በህክምና ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል።
የጤና ሚኒስቴር በትናንትናው ዕለት በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 2 ሰዎች በማርበርግ ቫይረስ መያዛቸውን ማስታወቁ አይዘነጋም።
