በማርበርግ ቫይረስ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ተጨማሪ ሁለት ሰዎች ቫይረሱ ተገኝባቸዉ

Date:

በዛሬው ዕለት ከተደረጉ 13 የላብራቶሪ ምርመራዎች ተጨማሪ 2 ሰዎች ላይ የማርበርግ ቫይረስ መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዛሬው ዕለት በተደረገው ምርመራ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው ታማሚ ከዚህ በፊት ከተገለፀው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጂንካ ከተማ በለይቶ ማቆያ የነበሩ ሲሆኑ በተመሳሳይ ቦታም የህክምና ክትትላቸውን እያደረጉ እንደሚገኙ ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በተጨማሪም በዛሬው ዕለት አንድ ሰው በቫይረሱ ህይወቱ ሲያልፍ በአጠቃላይ በቫይረሱ ህይወታቸው እንዳለፈ የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር አራት መድረሱ ተጠቁሟል።

በሽታው መከሰቱ ከተገለጸበት ቀን አንስቶ እስካሁን 46 የላብራቶሪ ምርመራዎች የተከናወኑ ሲሆን በአጠቃላይ ቫይረሱ በ8 ሰዎች ላይ መገኘቱ ተመላክቷል። እንዲሁም አራት ሰዎች ደግሞ በህክምና ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል።

የጤና ሚኒስቴር በትናንትናው ዕለት በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 2 ሰዎች በማርበርግ ቫይረስ መያዛቸውን ማስታወቁ አይዘነጋም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...