በማንችስተር ደርቢ የኳታር የጸጥታ ሀይሎች ይሳተፋሉ

Date:

ዛሬ ምሽት 12:30 ላይ በታላቁ ኦልድ ትራፎርድ ስታዲየም በሚደረገው የማንቹሪያን ደርቢ ላይ የኳታር የጸጥታ ሀይሎች በደህንነት ስራ ላይ እንደሚሳተፉ ተነገሯል።

የማንቹሪያን ደርቢ ጨዋታ ተጠባቂ ሲሆን ባለሜዳዉ ማንችስተር ዩናይትድ ወደ ወራጅ ቀጠናዉ ዝቅ ላለማለት ለሲቲዝኖቹ ደግሞ የሻምፒዮንስ ሊግ መግቢያ ቦታ ለማግኘት የሚያደርጉት ጨዋታ ይሆናል።

ምንም እንኳ ማንችስተር ዩናይትድ ከታላላቅ ቡድኖች ጋር በሚያደርገዉ ጨዋታ ጠንካ መሆኑን ደጋግሞ ቢያሳይም ከነበረበት የከፍታ ደረጃ ከወረደ ግን አመታት ተቆጥረዋል። ዩናይትድ በማንቹሪያን ደርቢ የበላይነት የያዘዉ ቡድንም ነዉ።

በደርቢዉ ጨዋታ ላይ በማንችስተር ሲቲ በኩል ኤርሊንግ ሃላንድ በጉዳት የማይገኝ ሲሆን ዩናይትድ ማቲያስ ዲሊግትን እንደሚያጣዉ ተዘግቧል።

በጽጥታ ስራዉ ላይ ይሳተፋሉ ለተባሉት የኳታር የጸጥታ ሀይሎችም የማንችስተር ከተማ ፖሊስ ገለጻና መመሪያ ሰጥቷቸዋል።

 

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...