በምሥራቅ አፍሪካ የሚስተዋሉ ሽብርተኝነትንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል የቀጣናው ሀገራት የመረጃ ትብብር ወሳኝ ነው

Date:

በምሥራቅ አፍሪካ የሚስተዋሉ ሽብርተኝነትንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል የቀጣናው ሀገራት የመረጃ ትብብር ወሳኝ መሆኑን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ታዜር ገብረእግዚአብሔር ገለጹ።

የአፍሪካ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ኮሚቴ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ታዜር ገብረእግዚአብሔር በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በመረጃ ትብብር የቀጣናውን ደህንነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ይመክራል።

ሽብርተኝነት፣ ጽንፈኝነት እና ሌሎች ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ዛሬም ድረስ የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ስጋት ሆነው መቀጠላቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም በቀጣናው ያለውን የደህንነት ስጋት በመቆጣጠር ሰላም ለማስፈን በሀገራት መካከል የተቀናጀ የመረጃ ትብብር ያስፈልጋል ብለዋል።

የምሥራቅ አፍሪካ የመረጃና ደህንነት ተቋማት ስብሰባ፥ ቀጣናዊ ትብብሩ በተግባር የሚፈጸምበትን እድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

የጸጥታ ስራ የጋራ ትብብርን የሚጠይቅ ነው ያሉት አቶ ታዜር፤ ተቋማቱ ፈጠራን የተከተለና የህግ ማዕቀፍን ታሳቢ ያደረገ ቅንጅት መፍጠር አለባቸው ብለዋል።

የአፍሪካ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ኮሚቴ ዋና ፀሐፊ ጃክሰን ሀማታ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ኮሚቴ ዓላማው የቀጣናውን ደህንነት በጋራ ለመጠበቅ ትብብርን መፍጠር መሆኑን ገልጸዋል።

የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት በመረጃ ላይ የተመሰረተ ቅንጅት በመፍጠር ሽብርተኝነትንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን መከላከል እንዳለባቸው ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...