በሱዳን ላይ 4ተኛ ዙር ማእቀብ ተጣለ

Date:

የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት በሱዳን ላይ 4ተኛ ዙር ማእቀብ መጣሉን አስታወቀ፡፡ ምክር ቤቱ ዛሬ ባከናወነው ስብሰባው ማእቀብ የጣለው በሁለት ግለሰቦችና ሁለት ተቋማት ላይ ነው፡፡

‹‹በሱዳን ውስጥ ከተፈጠረው የሰብአዊ መብት ጥሰትና ከአገሪቱ ሰላምና መረጋጋት መደፍር ጋር በተያያዘ›› በሚል ማእቀብ የተጣለባቸው ሁለት ተቋማት አልካላጂ ባንክና ሬድ ሮክ ማእድን ኩባንያ ናቸው፡፡

የአውሮፓ ህብረት እንዳለው አልካላጂ ባንክ የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ዋና አዛዥ ጄኔራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ ቤተሰቦች ሰፊ የባለቤትነት ድርሻ የያዙበት ሲሆን በጦርነቱ ወቅትም ለፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ እንቅስቃሴ ወሳኝ የፋይናንስ ምንጭ ነው፡፡

ሬድ ሮክ ማእድን ኩባንያ ደግሞ ለሱዳን ጦር ሀይል ጦር መሳሪያዎችንና ተሸከርካሪዎችን በማምረት ትልቅ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አስረድቷል፡፡ የአውሮፓ ህብረት ዛሬ ማእቀብ የጣለባቸው ግለሰቦች ደግሞ አቡ አቅላ መሀመድና ሁሴን ባርሻም ናቸው፡፡

አቡ አቅላ መሀመድ የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ኮማንደር የነበሩ ሲሆን ከድተው የመንግስትን ጦር ሀይል የተቀላቀለሉ ሲሆኑ ሁሴን ባርሻም ደግሞ የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ወታደራዊ መሪ ናቸው፡፡

እነዚህ ግለሰቦች በአውሮፓ የሚገኝ ገንዘባቸው እንዳይንቀሳቀስ የተደረገ ከመሆኑም በላይ የቪዛ ማእቀብ እንደተጣለባቸውም ምክር ቤቱ አስረድቷል፡፡ የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ከዚህ ቀደም ከሱዳን ጦርነት ጋር በተገናኘ 3 ጊዜ ማእቀቦችን መጣሉ የሚታወስ ነው፡፡

(ዘ-ሐበሻ ዜና)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እናት ፓርቲ የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን “የእነ አጼ በጉልበቱ መፈንጫ” ሲል ኮነነ ውጤቱንም እንደማይቀበል አስታወቀ

እናት ፓርቲ በቅርቡ የተካሄደውን የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ አጠቃላይ ሂደትና...

የምክክር ኮሚሽኑ መዝጊያ

የኦሮሚያ ክልል ያቃረበውን ቅሬታ የተመለከተው የአሸማጋይ ቡድን አዲስ አበባ...

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...