በአሜሪካን ሀገር የተሰራው “ሊያ” ፊልም ሊመረቅ ነው

Date:

በተዋናይት ደራሲና ፕሮዲዩሰር ቅድስ ባየልኝ ተጽፎ የተዘጋጀው “ሊያ” ፊልም ሊመረቅ ነው፡፡

በፊልሙ ላይ ተወዳጅና አንጋፋ የሆኑት ተዋናይ ወለላ አሰፋ፣ ግሩም ኤርሚያስ፤ ቅድስት ባየልኝ፣ ዲጄ ሉና እና ሌሎች እንደተሳተፉበት ተገልጿል።

የኢትዮ ውድ ኢንተርቴይመንት የኢትዮጵያ ተወካይ የፊልሙ ረዳት ዳይሬክተር ፊልሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ ሶስት አመት የፈጀ መሆኑን እና  በወጪ ደረጃ ከ35 ሺ በላይ የአሜሪካን ዶላር መፍጀቱን ገልጿል።

ፊልሙ የፊታችን ሀምሌ 10/2017 ዓ/ም ከምሽቱ 12:00 ሰዓት በአለም ሲኒማ በታላቅ ድምቀት እንደሚመረቅ ሀምሌ 3/2017 ዓ/ም በግዮን ሆቴል በተሰጠ መግለጫ ተነግሯል፡፡

ፊልሙን በመጻፍ እና በማዘጋጀት የተሳተፈችው ቅድስ ባየልኝ  ከዚህ ቀደም ህይወት እንደዋዛ፣ እጸበለስና ከአትላንቲክ ባሻገር የተሰኙ ፊልሞችን በመድረስ፣ በመተወንና በማዘጋጀት ተሳትፎ ማድረጓ ይታወሳል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...

ባለሙያ ባልሆኑ ግለሰቦች የሚሰራጭ የተዛባ መረጃ በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነዉ

የሳይካትሪስት የሙያ ፈቃድና ሥልጠና የሌላቸው ግለሰቦች በተለያዩ መገናኛ...

የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ...

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...