በአረብ ሀገራት ተሰደው የሚሰሩ  ኢትዮጵያዊያን የቤት ሰራተኞችን ጤና እና ደህንነት ለማሻሻል ያለመ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

Date:

በኢትዮጵያ በስደትና ጤና ላይ የተደረጉ የምርምር ጥናቶች አነስተኛ በመሆናቸው ከፍልሰት ጋር የተገናኙ ችግሮችን ለመፍታት ትልቅ ክፍተት እንደሚፈጥር ተጠቁሟል። የኢትዮጵያዊያን ስደተኛ የቤት ሰራተኞችን ጤና እና ደህንነት ለማሻሻል ያለመ ፕሮጀክት ይፋ ሆኗል፡፡

INNOVETH የተሰኘው  የዚህ ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ ዶ/ር ካሳሁን ሃብታሙ እንደተናገሩት ወደ ተለያዩ የአረብ ሀገራት ለስራ የሚያቀኑ ሴት ኢትዮጵያዊያን በርካታ ችግሮች ያጋጥማቸዋል።

የቋንቋ፣የባህል ተፅእኖ፣የአየር ንብረት ለውጥን ተከትሎ ለስነ አእምሮ እና ለስነተዋልዶ ጤና ችግሮች እንደሚዳረጉ ጠቁመዋል።

እንዲህ ያለ ችግር የሚያጋጥማቸው ሴቶች በቂ የሆነ የጤና አገልግሎትን እንደማያገኙ አስተባባሪው ገልፀው ይህን ክፍተት ለመሙላት እንዲቻል ፕሮጀክቱ ይፋ ሆኗል።

ፕሮጀክቱ በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኛ የቤት ሰራተኞችን ጤና እና ደህንነት በቴክኖሎጂ ፈጠራ በመታገዝ ለማሻሻል ያለመ መሆኑን ዶክተር ካሳሁን ጨምረው ተናግረዋል።

የሞባይል አፕልኬሽንን በመጠቀም እና የባለሙያዎችን ቡድን ባካተተ መልኩ ስደተኞች ባሉበት ቦታ መረጃ ማግኘት የሚችሉበት እድል ተመቻችቶላቸዋል።

የሚገጥማቸውን የጤና ችግሮች በተለይም የስነ አእምሮና የስነልቦና ጉዳቶችን ማሻሻል እንዲችሉ የሚያስችላቸውን መረጃ እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ተብሏል።በተጨማሪም ወደ አረብ ሀገራት ጉዞ ከመጀመራቸው አስቀድሞ አስፈላጊውን ስልጠና እንዲያገኙ ይደረጋል ሲሉ አሰተባባሪው ገልፀዋል።

ብስራት ራዲዮ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...