በአዲስ አበባ የ6ኛ እና የ8ኛ የሚኒስትሪ ተፈታኞች አፋን ኦሮሞ እንደሚወስዱ ተገለጸ

Date:

ውሳኔው ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤቶችንም ያካትታል ተብሏል

ዘንድሮ በአዲስ አበባ በሚሰጡ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተናዎች አፋን ኦሮሞ እንደሚካተት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በአዲስ አበባ ለሚገኙ አሥራ አንዱም ክፍላተ ከተሞች የትምህርት ጽሕፈት ቤቶች ማሳወቁን ሪፖርተር የተመለከተው ደብዳቤ ያሳያል። ደብዳቤው በመንግሥት፣ በግልና በዓለም አቀፍ (International) አስፈታኝ ትምህርት ቤቶቹም ዝግጅት እንዲያደርጉ ያሳስቧል፡፡

ለ8ኛ ክፍል አማርኛና አፋን ኦሮሞ እንደ አንደኛ ቋንቋ እንደሚሰጡ በደብዳቤው ሲመላከት የሒሳብ ፣ የእንግሊዝ ፣ የሳይንስና የዜግነት (ግብረገብ) ትምህርቶችም ይሰጣሉ ይላል ።

የ6ኛ ክፍል ፈተና በአማርኛ ሥርዓተ ትምህርት ለሚያስተምሩ ትምህርት ቤቶች አማርኛ እንደ አንደኛ ቋንቋ ሲሰጥ፤ አፋን ኦሮሞ ደግሞ እንደ ሁለተኛ ቋንቋ ይሰጣል፡፡

የ6ኛ ክፍል ፈተናን በአፋን ኦሮሞ ሥርዓተ ትምህርት ለሚያስተምሩት ደግሞ አፋን ኦሮሞ እንደ አንደኛ ቋንቋ ሲሰጥ፣ አማርኛ እንደ ሁለተኛ ቋንቋ ይስጣል፡፡ ሌሎች የትምህርት ዓይነቶች ሒሳብ፣ እንግሊዝኛ፣ አካባቢ ሳይንስና ግብረገብ ተመሳሳይ ናቸው፡፡

ደብዳቤውን የፈረሙት የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዲናኢል ጫላ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ ተጠይቀው፣ «ጉዳዩ የሚመለከተው ሌላ ስው ነው፤›› ብለዋል፡፡ የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት አቶ አበበ ደግሞ፣ ‹‹ስለጉዳዩ ማጣራት ይኖርብኛል›› በማለት ዝርዝር መግለጫ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ሪፓርተር ጋዜጣ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...