ኢትዮጵያ እና የናጀሪያው ኢንሳይት ዳይናሚክስ ሪሶርስስ Gas-by-Rail Economic Corridor Initiative ለማሳደግ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና ኢንሳይት ዳይናሚክስ ሪሶርስስ Gas-by-Rail Economic Corridor Initiative ለማሳደግ የመግባቢያ ስምምነት (MoU) በይፋ ተፈራርመዋል፣
በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሁለገብ አዳራሽ የተካሄደው የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን፣ ከውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ከአጋር ተቋማት የተውጣጡ ተወካዮችን እና ባለድርሻ አካላትን አሰባስቧል።
በኢትዮጵያ በኩል የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ባሬኦ ሃሰን እና የኢንሳይት ዳይናሚክስ ሪሶርስን ወክለው ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሙሳ ኢብራሂም ኩቺ ስምምነቱን ፈርመዋል።
ክቡር አቶ በረኦ ሀሰን ስምምነቱ ከኢትዮጵያ አረንጓዴ ትራንስፖርትን የማስፋፋት አገራዊ አጀንዳ ጋር የሚጣጣም መሆኑን ገልጸዋል ።
ስምምነቱ በነዳጅ ምትክ የታዳሽ ኃይል እና የተፈጥሮ ጋዝ አጠቃቀምን በማበረታታት፣ ፕሮጀክቱ ለአየር ንብረት ቅነሳ ጥረቶች አስተዋጽኦ የሚያደርግ ሲሆን ከ40 በላይ ከሰሃራ በታች ባሉ ሀገራት በባቡር ትራንስፖርት በማገናኘት አህጉራዊ ውህደትን ያሻሽላል ተብሎ ይጠበቃል።
በቀጣይ ወራት በአዲስ አበባ ከመላው አፍሪካ ከ 1000 በላይ ተሳታፊዎችን ያካተተ የንግድ ጉባኤ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ለማካሄድ ተግባብተው ስምምነት ተፈራርመዋል ።
