በኢራን ከአርብ ጀምሮ ከ450 በላይ ሰዎች ተገድለዋል

Date:

በኢራን የሚገኝ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት እስራኤል ጥቃት ከጀመረችበት አርብ ጀምሮ የደረሱ ጉዳቶችን ሲከታተል መቆየቱን ገልጿል።

እንደ ሰብዓዊ መብት ድርጅቱ ዘገባ ከሆነ 224 ንፁሀን ዜጎች ሲገደሉ 188 ቆስለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ 109 የኢራን ጦር ሠራዊት አባላት ሲገደሉ 123 ደግሞ ቆስለዋል ብሏል።
እስካሁን ማንነታቸው ያልታወቁ 119 ሰዎች መገደላቸውን እና 335 መቁሰላቸውን የሰብዓዊ መብት ድርጅቱ አስታውቋል።

ይህም የሰብዓዊ መብት ድርጅቱ የመዘገባቸው ሞቶችን ቁጥር 452 ሲያደርሰው 646 ቆስለዋል ብሏል።

የኢራን መንግሥት መገናኛ ብዙኃን እስካሁን በእስራኤል ጥቃት ስለተገደሉት ሰዎች መንግሥት ከገለፀው ውጪ ምንም ያሉት ነገር የለም።
BBC Amharic

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...