የልብ ቀዶ ህክምና ሀኪሙ እና የቀዶ ጥገና ቡድኑ መሪ ዶክተር ፈቀደ አጉዋር ለአዛውንቷ የተደረገው የደም ቧንቧዎችን የመክፈትና የልብ በርን የመቀየር ቀዶ ህክምና በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን በማህበራዊ ትሥሥር ገፃቸው አስነብበዋል።
ቀዶ ጥገናውን ለየት የሚያደርገው ሁለት የተለያዩ የደም ስሮችን መክፈት የሚያካትቱ ሁለት የተለያዩ ትልልቅ ቀዶ ህክምናዎች መከናወናቸው ነው ብለዋል።
ሰባት ሰዓታት የፈጀው ህክምና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ በአሁኑ ሰዓት የእድሜ ባለፀጋዋ በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ዶክተሩ አመልክተዋል፡፡
