14 ሚሊዮን ሰዎችን የሞት አደጋ ላይ የጣለው የትራምፕ ውሳኔ

Date:

አሜሪካ ለሃገራት የምትሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ የማቆም እርምጃ እ.ኤ.አ. በ2030 ከ14 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ለሞት ሊዳርግ እንደሚችል ዘ ላንሴት የህክምና መጽሄት ላይ የወጣ ጥናት አመልክቷል።

ያለጊዜያቸው ለሞት ከሚዳረጉት ውስጥ አንድ ሶስተኛው ህጻናት መሆናቸውን ጥናቱ ያመላከተ ሲሆን፣ “ለብዙ ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ላላቸው ሃገሮች ይህ ክስተት ከዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ወይም ከታላላቅ የትጥቅ ግጭት ጋር ሊወዳደር ይችላል” ጥናቱን ያዘጋጁት ዴቪድ ራሴላ ።

አክለውም “አሜሪካ የምታደርገው የገንዘብ ድጋፍ ለሁለት አስርት ዓመታት በጤና ላይ በተጋላጭ ህዝቦች መካከል ያለውን እድገት በድንገት የመቆም እንዲሁም ወደ ኋላ የመመለስ አደጋን ይቀንሳል” ሲሉ ገልጸዋል ።

ከ133 ሀገራት የተገኘው መረጃም እንደሚያሳየው የዩኤስኤአይዲ የገንዘብ ድጋፍ ከ2001 እስከ 2021 ባለው ጊዜ ውስጥ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት የ91 ሚሊዮን ሰዎችን ከሞት መታደግ መቻሉን የጥናት ቡድኑ ገልጾል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በመጋቢት ወር የፕሬዚዳንት ትራምፕ አስተዳደር በዩኤስ ዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ ወይም ዩኤስኤአይዲ ከ 80% በላይ ፕሮግራሞችን መሰረዙን ማስታወቃቸው የሚትታወስ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...