ሚንስቴሩ ግንቦት 16 በበሽታው የተያዘ የመጀመሪያውን ታማሚ መገኘቱን ይፋ ካደረገ በኋላ እስከ ሐምሌ 2 ድረስ ለ520 በበሽታው ለተጠረጠሩ ሰዎች የላብራቶሪ ምርምራ ማድረጉን አስታውቋል፡፡
የጤና ሚኒስቴር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በበሽታው ዙሪያ በሰጡት መግለጫ በምርመራው 26 ሰዎች በሽታው እንደተያዙ ተረጋግጧል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም አንድ ታማሚ በበሽታው ህይወቱ አልፏል፣ ቀሪዎቹ 25 ታማሚዎች ሙሉ በሙሉ ከበሽታው ማገገማቸውን ገልጸዋል፡፡
ሚኒስቴሩ ህብረተሰቡ ለበሽታው አጋላጭ ከሆኑ መንገዶች በመጠንቀቅ እና የመከላከያ መንገዶችን ችላ ሳይል በመተግበር የበሽታውን ስርጭት በዘላቂነት እንዲገታ ጥሪ አቅርቧል።
