በኢትዮጵያ ፈር ቀዳጅ በመሆን ከ11 ዓመታት በፊት የተሟላ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ በአሁኑ ጊዜ ከ7.3 ሚሊዮን በላይ አስቀማጭ ደንበኞችን በማፍራት የተቀማጭ ገንዘቡን ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ ማድረስ ችሏል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ተቀማጭ ገንዘብ ከኢንዱስትሪው የ51.3 በመቶ ድርሻ መያዝ ችሏል።
ባንካችን በሲቢሲ ኑር ከወለደ ነፃ የባንክ አገልግሎት ባለፉት 11 ዓመታት ከ150 ቢሊዮን ብር በላይ በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ለተሠማሩ ደንበኞች የፋይናስ አቅርቦት ያደረገ ሲሆን፣ በአሁኑ ጊዜ በዚሁ ዘርፍ ተሰጥቶ የሚገኘው ጠቅላላ የብድር መጠን ከ79.2 ቢሊዮን ብር በላይ ነው።
ባንካችን ከወለድ ነፃ ፋይናንሲንግ ዘርፉም የኢንዱስትሪውን 48 በመቶ ድርሻ በመያዝ በመምራት ላይ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዚህ ስኬት ላበቁን ደንበኞች እና ሁሉም ባለድርሻ አካላት ምስጋናውን ያቀርባል።
