ንግድ ባንክ በሲቢኢ ኑር  የሰበሰበው ገንዘብ ከ200 ቢሊዮን ብር አለፈ

Date:

በኢትዮጵያ ፈር ቀዳጅ በመሆን ከ11 ዓመታት በፊት የተሟላ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ በአሁኑ ጊዜ ከ7.3 ሚሊዮን በላይ አስቀማጭ ደንበኞችን በማፍራት የተቀማጭ ገንዘቡን ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ ማድረስ ችሏል። 

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ተቀማጭ ገንዘብ ከኢንዱስትሪው የ51.3 በመቶ ድርሻ መያዝ ችሏል።

ባንካችን በሲቢሲ ኑር ከወለደ ነፃ የባንክ አገልግሎት ባለፉት 11 ዓመታት ከ150 ቢሊዮን ብር በላይ በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ለተሠማሩ ደንበኞች የፋይናስ አቅርቦት ያደረገ ሲሆን፣ በአሁኑ ጊዜ በዚሁ ዘርፍ ተሰጥቶ የሚገኘው ጠቅላላ የብድር መጠን ከ79.2 ቢሊዮን ብር በላይ ነው።

ባንካችን ከወለድ ነፃ ፋይናንሲንግ ዘርፉም የኢንዱስትሪውን 48 በመቶ ድርሻ በመያዝ በመምራት ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዚህ ስኬት ላበቁን ደንበኞች እና ሁሉም ባለድርሻ አካላት ምስጋናውን ያቀርባል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...