በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች የክልሉ መንግሥት የትርፍ ሰዓት ክፍያዎችን በቅርቡ በተደረገው የደመወዝ ማሻሻያ መሠረት እንዲያሰላ ጠየቁ። ባለሙያዎቹ ጥያቄውን ያቀረቡት የፌዴራል መንግሥት በመላ ሀገሪቱ ወጥ የሆነ የክፍያ ሥርዓት እንዲኖር ካወጣው መመሪያ ጋር በተጣጣመ መልኩ እንዲተገበር መሆኑ ተገልጿል።
በባሌ ሮቤ አጠቃላይ ሆስፒታል የሚገኝ አንድ የጤና ባለሙያ ለአዲስ ስታንዳርድ፣ ጥያቄያቸው የተሻሻለውን የደመወዝ መዋቅር መሠረት በማድረግ የሚከናወኑ የሥራ ክፍያዎችን የሚገዛውን ብሔራዊ መመሪያ ተግባራዊ ለማድረግ መሆኑን ገልጸዋል።
“ለአዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ የሚሆን በጀት የለም ተብለናል። ለሁለት ወራት በአዲሱ ደመወዝ መሠረት የትርፍ ሰዓት ክፍያ አግኝተን ነበር፣ ከዚያ በኋላ ግን ክፍያው ተቋርጧል” ሲል ባለሙያው ተናግሯል።
በጉደር ሆስፒታል የሚገኝ አንድ ሐኪም በተመሳሳይ ሁኔታ የመስከረም እና ጥቅምት ወራት የትርፍ ሰዓት ክፍያዎች በአዲሱ ደመወዝ መሠረት መሰጠታቸውን ያረጋገጠ ሲሆን፣ ሆኖም የሆስፒታሉ አመራሮች በኋላ ላይ ተጠርተው ክፍያውን በ“በአዲሱ ደመወዝ” መሠረት እንዳይፈፀም መመሪያ እንደተሰጣቸው ሐኪሙ ገልጿል።
የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ኃላፊ ፕሮፌሰር ነፃነት ወርቅነህ ለአዲስ ስታንዳርድ በሰጡት ምላሽ፣ ውሳኔው በክልል ደረጃ የተላለፈ መሆኑን ገልጸው ስለ ዝርዝሩ ግን ተጨማሪ ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም።
