የኮሎምቢያ ፖለቲከኞችን ያሳፈረ አዉሮፕላን ተከሰከሰ

Date:

በቬኔዙዌላው ድንበር አቅራቢያ በተከሰከሰው አዉሮፕላን ፖለቲከኞች እና የህግ አዉጪ ባለሙያዎችን ጨምሮ የ15 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተዘግቧል።

ከሟቾቹ መካከል የ36 ዓመቱ የኮሎምቢያ የተወካዮች ምክር ቤት የካታቱምቦ ክልል ተወካይ የሆኑት ዲዮጀነስ ኩንቴሮ አማያ ይገኙበታል ተብሏል።

በመጋቢት ወር ሊካሄድ በታቀደው የኮንግረስ ምርጫ እጩ የነበሩት ካርሎስ ሳልሴዶ በአዉሮፕላኑ አደጋ ህይወታቸዉ ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል።

የአዉሮፕላን አደጋዉን ምክንያት ለመመርመር አደጋዉ የደረሰበት አካባቢያዊ መልክአምድር አስቸጋሪ መሆኑን የአካባቢው ባለስልጣናት እየተናገሩ ሲሆን፤ ይህ የነፍስ አድን ስራዉን እንደገታዉ ገልፀዋል።

ባለሥልጣናቱ የአደጋውን መንስኤ እስካሁን ያልገለጹ ሲሆን፤ የአውሮፕላኑ የድንገተኛ አደጋ መብራት አደጋዉ ከመከሰቱ በፊት እየሰራ አልነበረም ተብሏል።

የኮሎምቢያ የትራንስፖርት ሚኒስቴር አውሮፕላኑ በቦታው ከተገኘ በኋላ፤ ባለሥልጣናቱ በሕይወት የተረፉ አለመኖራቸውን በሚያሳዝን ሁኔታ መረጋገጡን በመግለጫ ገልፀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...