በዘንድሮው የአክሱም ጽዮን ክብረ በዓል 2 ሚ. ታዳሚዎች ይጠበቃሉ

Date:

“የፀጥታ ሃይሉ በመጠናከሩ ምንም የሚያሰጋ ነገር የለም”

በየዓመቱ በድምቀት በሚከበረውና የበርካታ ቱሪስቶች መስህብ በሆነው የአክሱም ጽዮን የንግስ ክብረ በዓል ላይ ዘንድሮም 2 ሚሊየን ገደማ ሰዎች ይታደማሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የአክሱም ከተማ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገብረ መድኀን ፍፁምብርሃን ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል፡፡

ጽ/ቤቱ ለበዓሉ ከሁለት ወራት በፊት ዝግጅት መጀመሩን የጠቆሙት ኃላፊው፤ ክብረ በዓሉን የሚያስተባብሩ የተለያዩ ኮሚቴዎች መዋቀራቸውንና የተለያዩ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በዓሉን ለመታደም ከኢትዮጵያ ውጭ ከሚመጡ ዜጎች ባሻገር በርካታ ቁጥር ያላቸዉ ከተለያዩ ክልሎች የሚመጡ ተሳታፊዎች መኖራቸውን የገለጹት ኃላፊው፤ በዚህም ህዳር 17 እና 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከአማራ ክልል 12 አውቶብሶች እንግዶችን ይዞ እንደመጣና በተመሳሳይ ከሐረርና ድሬደዋ የሚመጡትን ተሳታፊዎችም በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

ጽ/ቤቱ ለእንግዶቹ ማረፊያ ት/ቤቶችንና ሆቴሎችን ያዘጋጀ መሆኑን፣ በቀን ወደ ከተማዋ ይደረግ የነበረው በረራም ወደ 8 ከፍ መደረጉን በመጥቀስ የኢትዮጵያ አየር መንገድን አመስግነዋል፡፡ ክፍያውንም በሚመለከት “አምና አስከፍቶን ነበር፤ ነገር ግን ዘንድሮ 20 በመቶ ቅናሽ አድርጓል ” ብለዋል፡፡

ከዚህ ቀደም ባልተለመደ ሁኔታ ከበዓሉ ቀደም ብለዉ ባሉት ቀናት በርካታ ቁጥር ያለዉ ታዳሚ ዘንድሮ መመልከታቸዉን የገለጹት ኃላፊው፤ የሰላም ሁኔታውን በተመለከተ የፀጥታ ሃይሉ በመጠናከሩ ምንም የሚያሰጋ ነገር የለም ብለዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...