በደብረ ብርሃን ከካንፕ ውጪ ላሉ ተፈናቃዮች ከሦስት ወር በኃላ ድጋፍ ተደረገ

Date:

በደብረብርሃን የሚገኙ ተፈናቃዮች የተቋረጠባቸዉ ድጋፍ ከወራት በኋላ ማግኘት መቻላቸዉን ገለጹ።

ከኦሮሚያ ክልል ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው በደብረ ብርሃን የሚገኙ ተፈናቃዮች በቂ ደጋፍ እየተደረገላቸው አለመሆኑን ሲያነሱ ቆይተዋል።

ከዚህ ቀደም ለሃገሬ ቴሌቭዥን በቦታው የሚገኙ ተፈናቃዮቹን በማናገር ዘገባዎች ወደ እናንተ አድርሶ ነበር ፡፡

ከተፈናቅሉ 5ኛ አመታቸዉ ላይ እንደሚገኙ የገለፁት ጣቢያችን ያናገራቸው አስተባባሪዎች የመንግስት አካል እስካሁን አነጋግሯቸው እንድማያዉቅ ገልጸዋል፡፡  

ተፈናቃዮቹ ከሶስት ወር በኃላ አሁን ላይ ድጋፍ እንደተደረገላቸዉ በመግለጽ ድጋፉን ላደረጉላቸዉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

አሁንኑ ድጋፍ  ካለው ችግር አንጻር በቂ አለመሆኑንና በሁለትና በሶስት ወራት አንዴ የሚደረገዉ ድጋፍ በየወሩ እንዲደረግላቸዉና በቋሚነት የሚቋቋሙበት መንገድ እንዲያመቻችላቸዉ ጠይቀዋል፡፡

(ሀገሬ ቴቪ)፤

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...