” ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናውን ሲጨርስ Finish and Submit ሳያደርግ መውጣት የለበትም “

Date:

አጠቃላይ 190 ሺህ ተፈታኞች ፈተናቸውን በኦንላይን ይወስዳሉ።

የመጀመሪያ ቀን የኦንላይን ፈተና ውሎን ተከትሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

በዚህም ፤ ” ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናውን ሲጨርስ Finish and Submit ሳያደርግ መውጣት የለበትም ” ብሏል።

” ተፈታኙ ይህንን ማድረጉንም በፈተና ክፍሉ የተመደበ ባለሙያ ማረጋገጫ ሳይሰጠው እና ተፈታኙም ፈተናውን መጨረሱን በፊርማው ሳያረጋግጥ ከመፈተኛ ክፍል መውጣት አይኖርበትም ” ሲል አሳስቧል።

ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍል እንደገቡ ማሳወቅ እና ለዚህ ጉዳይ ተባባሪ ሆኖ ካልተገኙም በፈተና ማስፈጸሚያ ፕሮቶኮል መሰረት ተገቢው የእርምት ወይም አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ አዟል።

ሌላው ሚኒስቴሩ ፥ በተለያየ ምክንያት ” ሲስተም ዘጋብን ” በማለት ፈተና ክፍል ውስጥ የሚቀመጡ ተፈታኞችን በተለያዩ መንገዶች የማጣራት ሥራ በመስራት አስፈለጊውን የእርምት ወይም አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰድ እንደሚኖርበትም አሳስቧል።

ለምሳሌ፦ ስንተኛ ጥያቄ ላይ እንዳለ ወይም እንደዘጋበት / ባት መጠየቅ እና የተሰጠው መልስ ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር የሚጣረስ ሆኖ ከተገኘ በፈተና ማስፈጸሚያ ፕሮቶኮል መሰረት ተገቢውን እርምጃ እንዲወሰድ ብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...