ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ በጡረታ ከኃላፊነታቸው ተሰናበቱ

Date:

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያንና የአዲስ አበባ አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ፣ የሊቀ ጳጳስነት ኃላፊነታቸውን በጡረታ ምክንያት ማስረከባቸው ተሰማ።

ብፁዕነታቸው ያቀረቡትን ከኃላፊነት የመነሳት ጥያቄ የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዎ 14ኛ የተቀበሉት ሲሆን፣ ውሳኔው በቅድሥት መንበር ልዩ መልዕክተኛ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ አማካይነት ይፋ ሆኗል።

በብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ምትክ የቀድሞው የአዲስ አበባ አገረ ስብከት ረዳት ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ተስፋሥላሴ አዲሱ፣ የአዲስ አበባ አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተሹመዋል። ቤተክርስቲያኗ ባወጣችው ይፋዊ መግለጫ፣ አዲሱ ተሿሚ የአገረ ስብከቱን መንፈሳዊ አገልግሎት በበላይነት እንደሚመሩ ታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...