ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ የእንኳን ደስ አለዎ መልዕክት አስተላለፉ

Date:

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ለሊዮ 14ኛ ሊቀ ጳጳስ የእንኳን ደስ ያለዎ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ቅዱስነታቸው ለሊዮ 14ኛ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ሊዮ 14ኛ የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ በመሆን በመመረጣቸው የተሰማቸውን ልባዊ ደስታ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስም ገልጸው፤ “እንኳን ደስ አለዎ ለማለት እወዳለሁ” ብለዋል።

የምድራችን ችግር በልዩ ልዩ ፈተናዎች እየጨመረ የመጣ መሆኑን የጠቆሙት አቡነ ማትያስ፥ “በእግዚአብሔር ኃይል የተመረጡ ሰዎችና መሪዎች ችግሮቹን በቀላሉ ማሸነፍ እና ፍሬ ማፍራት ስለሚችሉ፤ ቅዱስነትዎ ፈተናዎችን በሙሉ በቀላሉ በማለፍ የቤተ ክርስቲያንዎን ተልእኮ በላቀ ስኬት እንደሚወጡ ተስፋ እናደርጋለን” ብለዋል።

አያይዘውም፥ “በአገልግሎትዎ ሁሉ እግዚአብሔር አምላክ ከጎንዎ እንዲሆን እመኛለሁ” ማለታቸውን ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...