ቲታስ ሕንፃን ቤተክርስቲያን ገዛችው

Date:

አዳማ ፖስታ ቤት የሚገኘው ቲታስ ሕንጻን ደብረ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ለሆስፒታል አገልግሎት ንብ ባንክ ባወጣው ጫረታ መሰረት ተወዳድሮ አሸንፎ ገዝቶታል። አዳማ ደብረ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል በር ላይ የሚገኘው ባለ 8 ወለል ቲታስ ሕንጻ በካቴድራሉ በር ላይ የሚገኝ ሲሆን ለሆስፒታል አገልግሎት እንደታሰበ የካቴድራሉ አስተዳዳሪ መልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ዜናማርቆስ ተናግረዋል።

ካቴድራሉ እንደ ሀገረ ስብከት ትልቅ ካቴድራል እና ብዙ ምእመናን የሚገለገሉበት ሲሆን ነገር ግን ራስ አገዝ ገቢ ማስገኛ አልነበረውም። አሁን ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ንብ ባንክ ባወጣው ጫረታ በመሳተፍ ካቴድራሉ አሸናፊ ሆኗል። ይህ ሲሆን ግን ሙሉ ክፍያ ለመክፈል የሚያስችል ብር አልነበረውም። ቅዱስ ገብርኤል ብዙ ልጆች እንዳሉት እና ይሄን መክፈል እንደሚቻል በማመን እንጂ።

በዚህም መሰረት ጥር 2 እስከ ጥር 5/2018 ዓ/ም ለተከታታይ 4 ቀናት በካቴድራሉ ግቢ ታላቅ መንፈሳዊ ባዛር ተዘጋጅቷል። መንፈሳዊ ባዛሩን የምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ባርከው አስጀምረውታል። የሀገረ ስብከቱ የመምሪያ ኃላፊዎች ፣የገዳማት እና የአድባራት አስተዳዳሪዎችም የዚህ ባዛር ተሳታፊ ሆነዋል።

ይህ መንፈሳዊ ባዛር ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት የሚቀጥል ስለሆነ በአዳማ እና በዙሪያው የምትገኙ የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች ለነፍሳችሁ ፈውስ ስታገኙበት የነበረው ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ነገ ደግሞ ስጋችሁን የምትፈወሱበትን ሆስፒታል እውን ለማድረግ እየተሰራ ስለሆነ የዚህ ስራ ተሳታፊ እንድትሆኑና በባዛሩ ላይ እንድትገኙ ጥሪ ተላልፏል።

Menker Media

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...