የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለንግድ ንግግሮች ተጨማሪ ጊዜ በመፍቀድ በአውሮፓ ህብረት ላይ ለመጣል ያቀዱትን የ50 በመቶ ቀረጥ እስከ ጁላይ 9 አራዝመዋል።
ትራምፕ ለድርድር ያን ያህል ፍላጎት እንደሌላቸው ቢገልጹም፤ ቀነ-ገደቡን ለማራዘም ግን ተስማምተዋል።
ትራምፕ የታሪፍ ጭማሪ ቀነ-ገደቡን ያራዘሙት ውሳኔው እንዲዘገይ ከጠየቁት የአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር ከተነጋገሩ በኋላ መሆኑ ተገልጿል።
ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን በኤክስ ገጻቸው ላይ ባጋሩት ጽሁፍ ከትራምፕ ጋር ጥሩ ውይይት እንዳደረጉ እና የአውሮፓ ህብረት በፍጥነት ለመንቀሳቀስ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
