የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ጦር ከአፍጋኒስታን መውጣቷን በዩናይትድ ስቴትስ ታሪክ ውስጥ እጅግ አሳፋሪ ሲሉ ጠቅሰውታል።
ለዚህም የፕሬዚዳንት ጆ ባይደንን አስተዳደርን ክፉኛ ተወቃሽ ማድረጋቸውን አል ጀዚራ ዘግቧል።
ትራምፕ በጋዜጣዊ መግለጫቸው ላይ በወቅቱ በስልጣን እኔ ብኖር ኖሮ “የመውጣት ስራው በጉልበት እና በክብር ይፈጸም ነበር” ሲሉ ተናግረዋል።
የድሮው ቤታችን ሲሉ የጠቀሱት በባግራም የሚገኘው የቀድሞ የአሜሪካ ጦር ሰፈር አሁን በቻይና ቁጥጥር ስር መሆኑን በቁጭት አንስተዋል።
አሜሪካ በጊዜው የወሰደችው ርምጃ “ትልቅ ስትራቴጂካዊ ስህተት” መሆኑንም ጠቁመዋል።
