የፍልስጤስሙ ሀማስ አሜሪካ እና እስራኤል መራሽ የውጭ ሀይል ወደ ጋዛ አይገባም ሲል አስጠነቀቀ።
እስራኤል ከጋዛ ጥቅልላ እስካልወጣች ድረስ ትጥቅ መፍታት የሚለው የማይታሰብ ነው ሲል ሀማስ በመሪው በካህሊድ መሻል በኩል መግለጫ ሰጥቷል።
በቅርቡ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ጄ ትራምፕ ጋዛን ይታደጋል በሚል የሰላም ቦርድ ማቋቋማቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ሀማስ ግን ቅሬታውን እያቀረበ ይገኛል ።
ወረራ እስካለ ድረስ ራስን መከላከል የፍልስጤማውያን ኩራት ነው ሲሉ በዶሃ (ኳታር) ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል ካህሊድ መሻል።
አክለውም ትጥቃችን ሊያስፈቱን እና እንደወንጀለኛ ሊቆጥሩን ለሚሞክሩት የምናስረክበው መሳሪያ የለም ሲሉ የሀማስ ከፍተኛ ባለስልጣን መሻል አስታውቀዋል።
የሀማስ ቅሬታ በመካከለኛው ምስራቅ ቀጠና ሌላ ውጥረት እንዳይፈጥር ስጋት መጋረጡን ፖለቲከኞች እየተናገሩ ነው።
ቲ አርቲ ወርልድ እንደዘገበው።
