ቼክ በአገር ዉስጥ ማተም እንደሚጀምር ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት አስታወቀ

Date:

በቅርቡ ባንኮች የሚጠቀሙበትና ሚስጥራዊነቱን የተጠበቀ ቼክ በአገር ዉስጥ ማተም እንደሚጀምር ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት አስታውቋል። በዚህም ሁሉም ባንኮች የሚጠቀሙበትን ሚስጥራዊነቱ የተጠበቀ እና ወጥነት እንዲሁም የራሱ መለያ ኮድ ያለዉ ቼክ በአገር ዉስጥ ለማምረት ድርጅቱ በሂደት ላይ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚዉ ሽታሁን ዋለ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል። በህትመቱ፤ እያንዳንዱ የባንክ ደንበኛ እና ባንክ የራሱ የሆነ መለያ ቁጥር እንደሚኖረዉና ህጋዊነቱን ለማረጋገጥም ቀላል የሆነ ቼክ ለማምረት እቅስቃሴ ላይ መሆናቸዉን ገልጸዋል። ለህትመቱ የሚረዱ አምስት ማሽኖች የሚያስፈልጉ ሲሆን፤ አራቱ አገር ዉስጥ መግባታቸዉ እና አንድ ከጀርመን አገር የሚገባ ማሽንን በመጠባበቅ ላይ መሆናቸዉን ሥራ አስፈጻሚዉ ተናግረዋል። ማሽኑን በስድስት ወራት ዉስጥ ለማስገባት እንደታቀደ እና እስከሚቀጥለው ዓመት ድረስም ህትመቱን ለመጀመር መታቀዱንም አንስተዋል። ለዚህም ድርጅቱ፤ አስፈላጊ የሆነ የመረጃ ልዉዉጥን ከባንኮች ጋር ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም የገለጹ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም በዉጭ አገር የሚከናወነዉ የቼክ ህትመት የአገር መረጃን ወደ ዉጭ እንዲወጣ ያስገደደ እንደነበርም አስረድተዋል። ሆኖም፤ አሁን ላይ ደረጃዉን የጠበቀ የቼክ ህትመት በአገር ዉስጥ ከተከናወነ ይህንን እና ከቼክ ጋር የተያያዙ ወንጀሎችን እንደሚያስቀርም ሥራ አስፈጻሚዉ ጨምረዉ ለራዲዮ ጣቢያው ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...