በአዲስአበባ ከተማ በመስቀል አደባባይ መነሻው እና መድረሻው ያደረገው በጉጉት የሚጠበቀው 18ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር ነገ በታላቅ ድምቀት ይካሄዳል
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የብዙዎችን ቀልብ የሳበው ሻምፒዮናው በልዩ ድምቀት ለማከናወን ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቀዋል ።
ፌዴሬሽኑ በሻምፒዮናው ዙሪያ ከአሰልጣኞች ፣ቡድን መሪዎች እና አትሌቲክስ ዳኞች ጋር ውጤታማ ውይይት አድርጓል ።
በሻምፒዮናው ላይ 3 ክልልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እና 21 ክለቦች የሚካፈሉ ሲሆን 156 ሴት እና 389 ወንድ በድምሩ 535 አትሌቶች በውድድሩ ላይ ይፎካከራሉ ።
የፌዴሬሽኑ የውድድር ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ብስራት ለጥይበሉ እና አትሌት አሸብር ደምሴ በጋራ ውይይቱን መርተውታል ።
ሻምፒዮናው ከጥዋቱ 12:30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በቀጥታ የሚተላለፍ ይሆናል።
