አሜሪካና ሳዑዲ አረቢያ የ600 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የንግድ ስምምነት 

Date:

አሜሪካና ሳዑዲ አረቢያ 600 ቢሊየን  የአሜሪካ ዶላር የሚያወጣ የንግድ ስምማነት በዛሬው ዕለት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን ዛሬ ለይፋዊ  የስራ ጉብኝት ሳዑዲ አረቢያ የገቡት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሳዑዲ አረቢያው አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማን ናቸው የተፈራረሙት።

ስምምነቱ ሳዑዲ አረቢያ በዓለም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዕከል ለመሆን ለያዘችው እቅድ አስፈላጊውን የቴክኖሎጂ ግብዓት ከአሜሪካ  የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ለማግኘት ያስችላታል።

የስምምነት ስነ-ስርዓቱን የአሜሪካ የቴክኖሎጂ አምራች ድርጅቶች  ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች በአካል ተገኝተው ታድመዋል።

ከቴክኖሎጂ ባለፈ አሜሪካ ለሳዑዲ አረቢያ የምታደርገውን የ142 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የጦር መሳሪያ ሽያጭ ስምምነቱ ያካትታል ተብሏል።

በዛሬው ዕለት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ያቀኑት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ በቀጣይ በወደ ኳታር እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በማቅናት በአጠቃላይ ከ1 ትሪሊዮን የአሜሪካ ዶላር  በላይ የሚሆን የንግድ ስምምነት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...