አሜሪካና ሳዑዲ አረቢያ 600 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የሚያወጣ የንግድ ስምማነት በዛሬው ዕለት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን ዛሬ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ሳዑዲ አረቢያ የገቡት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሳዑዲ አረቢያው አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማን ናቸው የተፈራረሙት።
ስምምነቱ ሳዑዲ አረቢያ በዓለም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዕከል ለመሆን ለያዘችው እቅድ አስፈላጊውን የቴክኖሎጂ ግብዓት ከአሜሪካ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ለማግኘት ያስችላታል።
የስምምነት ስነ-ስርዓቱን የአሜሪካ የቴክኖሎጂ አምራች ድርጅቶች ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች በአካል ተገኝተው ታድመዋል።
ከቴክኖሎጂ ባለፈ አሜሪካ ለሳዑዲ አረቢያ የምታደርገውን የ142 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የጦር መሳሪያ ሽያጭ ስምምነቱ ያካትታል ተብሏል።
በዛሬው ዕለት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ያቀኑት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ በቀጣይ በወደ ኳታር እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በማቅናት በአጠቃላይ ከ1 ትሪሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የሚሆን የንግድ ስምምነት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
