በዚህ ሳምንት ታክስን በተመለከተ በቀረበው ዕቅድ ላይ በአሜሪካ ከሚኖሩ ሰዎች ወደ ሌላ ሃገር የሚደረጉ ክፍያዎች (ሬሚታንስ) ላይ የ5 በመቶ ተብሎ ታክስ ለመጣል ታቅዷል ተብሏል።
በታክሱ አብዛኞቹ በአሜሪካ ዜጎች የሚፈፀሙ ዝውውሮች ባይካተቱም በሌሎች ሀገር ዜጎች እና አንዳንድ በአሜሪካ ዜጎች የሚላኩ ገንዘቦች ግን ታክሱ ይፈፀምባቸዋል።
በ2023 ብቻ በአሜሪካ የሚኖሩ ሰዎች ከ93 ቢሊየን ዶላር በላይ ሬሚታንስ ወደ ሀገሮቻቸው የላኩ ስለመሆኑ የዓለም ባንክ ሪፖርት ያሳያል።
እንደ ኬንያ፣ ጋና እና ናይጄሪያ ያሉ ብዙ ሬሚታንስ ተቀባይ የሆኑ አፍሪካውያንም በጉዳዩ ስጋት ገብቷቸዋል።
በእነዚህ ሀገራት ሬሚታንስ ከሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዝ ሲሆን ከሬሚታንስ የሚገኘው ገንዘብ አንዳንዴ በእርዳታ እና ኢንቨስትመንት መልኩ ከሚያገኙት ገንዘብ ጭምር እንደሚበልጥም ተነግሯል።
ኢትዮጵያ በ2023/24 ከሬሚታንስ 6 ቢሊየን ዶላር ያገኘች ሲሆን ታክሱ ተግባራዊ ከሆነ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታት ይሆናል።
