አሜሪካ ኤርትራ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ልታነሳ ነው !

Date:


የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፣ አሜሪካ ከኤርትራ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማሻሻል መንገዶችን እያሰላ መሆኑ ተሠማ። የፕሬዝዳንቱ አስተዳደር የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ማሱድ ቡሎስ፣ የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር አሜሪካ በኤርትራ ላይ የጣለቻቸውን የተወሠኑ ማዕቀቦች የማንሳት ሂደት ለመጀመር ፍላጎት እንዳለው ለውጭ ዲፕሎማቶች መናገራቸውን ከባለሥልጣናት መስማቱን ጠቅሶ ዎል ስትሪት ጆርናል ዘግቧል።

ሌሎች ባለሥልጣናት በበኩላቸው፣ አሜሪካ ከኤርትራ ጋር ግንኙነቷን ለማሻሻልና ማዕቀቦችን ለማንሳት የያዘችው እቅድ በግምገማ ሂደት ላይ መሆኑን መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል።

ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ፣ ኤርትራ በፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር ሥር ከአሜሪካ ጋር ግንኙነቷን ለማሻሻል ፍላጎት እንዳላት በተደጋጋሚ ሲገልጡ ቆይተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች”:-  ከዳኛ ፍሬሕይወት ሳሙኤል ጋራ ውይይት

ዳኛ ፍሬሕይወት ሳሙኤል በተለይ በ1997 ዓ.ም በተደረገው ምርጫ 97...

የ12ኛ ክፍል የፈተና ቀን ታወቀ

የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከሳልቫ ኬር ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አደረጉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት...

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአፍሪካ ኅብረት የሰው ሠራሽ አስተውህሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ ሆነው ተሾሙ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአኅጉር ደረጃ ዘርፉን እንዲመሩ...