አራተኛው የአፍሪካ ፋክትስ ሰሚት በሴኔጋል መካሄድ ጀመረ

Date:

በአፍሪካ የሚገኙ መረጃ አጣሪ ተቋማትና ኤክስፐርቶችን የሚያሳትፈው አመታዊው የአፍሪካ ፋክትስ ጉባዔ በሴኔጋል ዳካር ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

ለአራተኛ ጊዜ እየተካሄደ የሚገኘው ይህ ጉባዔ በአፍሪካ የመረጃ ተአማኒነት እንዲጎለብት የሚደረገው ጥረት አካል ሲሆን የመረጃ ማጣራት (fact checking) ልምድ እንዲስፋፋ እና እንዲጎለብት ምክክሮች የሚደረጉበት እንደሚሆን ይጠበቃል።

የሀሰተኛ መረጃ ዘመቻዎችን መመርመር፣ የሰው ሰራሽ አስተዉሎት (AI) ተፅእኖ፣ የተቀናጁ አሰራር አማራጮች፣ ሀሰተኛ መረጃ በግጭት አከባቢዎች እንዲሁም አካባቢ ሁኔታን ያማከሉ መፍትሄዎች የሚሉት የጉባዔው አበይት አጀንዳዎች ናቸው።

በተጨማሪም በጉባዔው በአፍሪካ የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን በመከላከል ረገድ ያሉ እድሎች እና ፈተናዎችን በተመለከተ ውይይቶች ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉባዔ በተለያዩ ቋንቋዎች የሚሰሩ መረጃ አጣሪ ተቋማት እና የሚዲያ አጠቃቀም ክህሎት ባለሙያዎች ተሳታፊ ናቸው። ኢትዮጵያ ቼክም በዚህ ጉባዔ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

በመጨረሻም ጉባዔው ለዉድድር ከቀረቡ የአመቱ የሀሰተኛ መረጃ ማጣራት ስራዎች አሸናፊዎች እውቅና እና ሽልማት በመስጠት እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።

@EthiopiaCheck

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...