አራተኛ ቀኑን በያዘው አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት ጦርነት ዐበይት ክስተቶች

Date:

አራተኛ ቀኑን የያዘው በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥቃት የተጀመረው የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት በርካታ የአካበቢውን አገራት ለኢራን ጥቃት አጋልጦ ቀጥሏል።

  • ዛሬ ማክሰኞ ከማለዳ ጀምሮ እስራኤል በቴህራን እና ቤይሩት “ወታደራዊ ዒላማዎች” ባለቻቸው ስፍራዎች ላይ “ተከታታይ የአየር ጥቃቶች” እየፈጸመች መሆኑን አስታውቃለች።
  • የሳዑዲ መከላከያ ሚኒስቴር በሪያድ በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ላይ በሁለት ድሮኖች ጥቃት መፈጸሙን እና መጠነኛ ጉዳት መድረሱን ገልጿል።
  • የኢራን መንግሥት መገናኛ ብዙኃን በባህሬን በሚገኘው የአሜሪካ አየር ኃይል ማዘዣ እና የሠራተኞች ሕንጻ ላይ ጥቃት መድረሱን ዘግበዋል።
  • የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማርኮ ሩቢዮ የአገሪቱ ጦር በኢራን ላይ የሚፈጽመው “ከባዱ ጥቃት ገና እየመጣ ነው” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
  • ጦርነቱ ከጀመረ ጊዜ አንስቶ ስድስት የአሜሪካ ወታደሮች ተገድለዋል።
  • በኩዌት የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በቀጠናው የተፈጠረን ውጥረት በመጥቀስ ዝግ መሆኑን አስታውቋል።
  • እስራኤል ወደ ሊባኖስ እግረኛ ጦሯን በማስገባት “ተጨማሪ ቁልፍ ስፍራዎችን” ልትቆጣጣር መሆኑን አስታውቃለች።
  • የዩኬው ጠቅላይ ሚኒስትር ሰር ኪር ስታርመር መንግሥታቸው ጥቃትን ተከትሎ በኢራን በሚመጣ የመንግሥት ለውጥ እንደማያምን ተናግረዋል። ዶናልድ ትራምፕ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተባባሪ አይደሉም ሲሉ ከስሰዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...