አራተኛ ቀኑን የያዘው በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥቃት የተጀመረው የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት በርካታ የአካበቢውን አገራት ለኢራን ጥቃት አጋልጦ ቀጥሏል።
- ዛሬ ማክሰኞ ከማለዳ ጀምሮ እስራኤል በቴህራን እና ቤይሩት “ወታደራዊ ዒላማዎች” ባለቻቸው ስፍራዎች ላይ “ተከታታይ የአየር ጥቃቶች” እየፈጸመች መሆኑን አስታውቃለች።
- የሳዑዲ መከላከያ ሚኒስቴር በሪያድ በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ላይ በሁለት ድሮኖች ጥቃት መፈጸሙን እና መጠነኛ ጉዳት መድረሱን ገልጿል።
- የኢራን መንግሥት መገናኛ ብዙኃን በባህሬን በሚገኘው የአሜሪካ አየር ኃይል ማዘዣ እና የሠራተኞች ሕንጻ ላይ ጥቃት መድረሱን ዘግበዋል።
- የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማርኮ ሩቢዮ የአገሪቱ ጦር በኢራን ላይ የሚፈጽመው “ከባዱ ጥቃት ገና እየመጣ ነው” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
- ጦርነቱ ከጀመረ ጊዜ አንስቶ ስድስት የአሜሪካ ወታደሮች ተገድለዋል።
- በኩዌት የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በቀጠናው የተፈጠረን ውጥረት በመጥቀስ ዝግ መሆኑን አስታውቋል።
- እስራኤል ወደ ሊባኖስ እግረኛ ጦሯን በማስገባት “ተጨማሪ ቁልፍ ስፍራዎችን” ልትቆጣጣር መሆኑን አስታውቃለች።
- የዩኬው ጠቅላይ ሚኒስትር ሰር ኪር ስታርመር መንግሥታቸው ጥቃትን ተከትሎ በኢራን በሚመጣ የመንግሥት ለውጥ እንደማያምን ተናግረዋል። ዶናልድ ትራምፕ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተባባሪ አይደሉም ሲሉ ከስሰዋል።
