በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ34ኛ ሳምንት መርሃ ግብር አርሰናል እና ክሪስታል ፓላስ ሁለት አቻ ተለያይተዋል።
ማምሻውን በኤምሬትስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጃኮብ ኪዎር እና ሊያንድሮ ትሮሳርድ ለመድፈኞቹ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል።
ኤቤሬቺ ኤዘ እና ጂን-ፍሊፕ ማቴታ ለክሪስታል ፓላስ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
ውጤቱን ተከትሎ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አርሰናል ነጥቡን ወደ 67 ከፍ አድርጓል።
ክሪስታል ፓላስ በ45 ነጥብ 12ኛ ደረጃን ይዟል።
