በትግራይ ክልል ሰሜን ምእራብ ዞን ፅምብላ በተሰኘ ወረዳ ልዩ ስሙ ደብረ አባይ በተባለ አካባቢ ተከሳሽ ወጣት ሓጎስ ሙላው ገብረማርያም በመባል የሚታወቅ ሲሆን ንብረትነቷ የአንድ ገበሬ የሆነችን ፍየል ምቹ ጊዜና ቦታ መርጦ አርዶ ለመብላት በመሞከርበት ወቅት የፀጥታ አካላትና የአከባቢው ማህበረሰብ በመቀናጀት በሰሩት ስራ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ግለሰቡ ፍየሏን አርዶ ለመብላት ያስፈልጉኛል ያላቸውኝ መሳርያዎችና ለማጣፈጫነት ያገለግላሉ ያላቸውን የተለያዩ ቅመማ ቅመሞችን አዘጋጆቶ ፍየሏን አርዶ ለመብላት በዝግጅት ላይ እያለ ነው የተያዘው።ታድያ ጉዳዩ ሲከታተል የቆየው የወረዳው ፍርድ ቤትም ግለሰቡ በ1 ዓመት ከ6 ወር እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ መስጠቱን ከዞኑ የፖሊስ መምርያ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
በተያያዘ ጉዳይ ሚያዝያ 9 ቀን 2017 ዓ/ም በ ዓዲ ዳዕሮ ወረዳ ከአንድ ገበሬ ሶስት ከብቶችን ሰርቀው ከአከባቢው ለመሰወር የሞከሩ ገብረ ካህሳይ ያይንሸትና ተስፋይ ንርአ ተወለ በመባል የሚታወቁ ሁለት ግለሰቦች የአከባቢው ማህበረሰብ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተከትሎም የወረዳው ፍርድ ቤት ሚያዝያ 14 ቀን 2017 ዓ/ም ባዋለው ችሎት ተከሳሾቹ በፈፀሙት ተግባር ጥፋተኛ ናቸው በማለት አንደኛ ተከሳሽ ገብረ ካህሳይ ያይንሸት በ7 ዓመት ከ8 ወር ፅኑ እስራት፣ ሁለተኛ ተከሳሽ ተስፋይ ንርአ ደግሞ በሰባት ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ መሰጠቱን ብስራት ሬዲዮ ዘግቧል።
በሚሊዮን ሙ
