የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የቪክቶር ዮኬሬሽን ዝውውር በሙሉ ስምምነት ማጠናቀቁን ዘ አትሌቲክ አረጋገጠ።
መድፈኞቹ ተጫዋቹን በ 63.5 ሚልዮን ዩሮ እና ተጨማሪ 10 ሚልዮን ዩሮ ክፍያ ለማስፈረም ተስማምተዋል።
ስዊድናዊው አጥቂ ቪክቶር ዮኬሬሽ አሁን ላይ የጤና ምርመራውን እንዲያደርግ ከስፖርቲንግ ሊዝበን ፍቃድ ተሰጥቶታል።
ተጨዋቹ በነገው ዕለት ወደ አርሰናል የሚያደርገውን ዝውውር ለማጠናቀቅ የጤና ምርመራውን ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ቪክቶር ዮኬሬሽ በአርሰናል ቤቴ ታሪካዊውን የቴሪ ሄንሪ 14 ቁጥር ማልያ ለብሶ እንዲጫወት እንደተዘጋጀለት ተገልጿል።
@tikvahethsport
