መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ከ75 ቀናት ኋላ ማምረት ጀመረ

Date:

በትግራይ ክልል መቀለ አቅራቢያ የሚገኘው መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ከ75 ቀናት በኋላ ስሚንቶ ማምረት መጀመሩን አስታወቀ።

መስቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ በግብአት ማውጫ ሳይት (ኳሪ ሳይት) ላይ አጋጥሞት በነበረው ችግር ምክንያት ላለፉት 75 ቀናት ምንም አይነት ምርት እያመረተ እንዳልነበር ጠቆመ።

አሁን ላይ ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላትና የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ስምምነት ላይ በመደረሱ ወደ ምርት መመለሱን ከተቋሙ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

የመሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ሙሉ በሙሉ ለምርት ማቆሙ ዋነኛ ምክንያቴ ለስሚንቶ ምርት የምጠቀምባቸው የተለያዩ ጥሬ እቃዎች በተለያዩ ምክንያቶች በአግባቡ እና በወቅቱ ማግኘት ስላልቻልኩ ነው ሲል መግለጹን ሐምሌ 13 ቀን 2017 ዓ.ም ላይ ባቀረብነው ዘገባ መግለጻችን ይታወሳል።

ፋብሪካው የጥሬ እቃ በማወጣባቸው አከባቢዎች እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን በጊዜያዊነት እና በዘላቂነት ለመፍታት ከሚመለከታቸው መንግታዊ እና ማህበረሰባዊ አካላት ጋር በመመካከር ለመፍታት ጥረት ባደርግም እስካሁን መፍትሔ ማግኘት አልቻልኩም ማለቱም በዘገባው ተካቷል።

ነገር ግን ጥሬ እቃ በሚያወጣባቸው አከባቢዎች እያጋጠሙት ስላሉ ችግሮች በይፋ የገለጸው ነገር አልነበረም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...