አርቴፊሻል የአካል ድጋፍ የሚሰጡ የሕክምና ባለሙያዎች እጥረት መኖሩ ተገለጸ

Date:

እንደ ሀገር የሰው ሰራሽ የአካል ድጋፍ የሚሰሩ እስፔሻሊስት የሕክምና ባለሙያዎች በከፍተኛ ሁኔታ እጥረት መኖሩን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ይህም የሆነበት ምክንያት ለስልጠና የሚወጣው ወጭ ከፍተኛ በመሆኑ ነው ተብሏል።

የጤና ሚኒስቴር የሰው ሀብት ልማት ዘርፍ መሪ ስራ አስፈፃሚ አሰግድ ሳሙኤል ለአሐዱ እንደተናገሩት፤ በተለያየ ሁኔታ አካላቸውን የሚያጡ እና የሰው ሰራሽ የአካል ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች የሚሰሩ እስፔሻሊስት የሕክምና ባለሙያዎች እጥረት ተከስቷል።

ይህን የሕክምና ስልጠና ይሰጥ የነበረው ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንደነበር ገልጸው በተለያየ ምክንያት የስልጠና ሂደቱ ተቋርጦ መቆየቱን አስታውቀው በአሁኑ ጊዜ ሕክምናውን ለማድረግ በተለያየ ምክንያት ፍላጎቱ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።

የተገልጋዩ ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የስልጠና ሂደቱን መጀመሩን አቶ አሰግድ ተናግረዋል።

ችግሩን ለመፍታት በክልል ደረጃ ስልጠናውን ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ አንስተው፤ የሚሰለጥኑ የሕክምና ባለሙያዎች የምልመላ ሂደትም መጠናቀቁን ገልጸዋል።

የጤና ስልጠና በፍላጎት ላይ የተመሰረተ ሲሆን፤ በየ ጤና ተቋሙ የሚሰጠው አገልግሎት የተለያየ መሆኑን ተጠቁሟል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ለጤና ባለሙያዎች ለሚሰጠው ስልጠና የበጀት እጥረት እና የሎጅስቲክ ችግር እየገጠመው መሆኑንም ሥራ አስፈጻሚው ጨምረው አስታውቀዋል።

የተፈጠረው የበጀት ችግር ለመፍታት በማህበራዊ ትስስር ስልጠና እየሰጠ ቢሆንም፤ የግድ በአካል ስልጠና መስጠት ሲፈልግ ችግር እንደሆነበት አስታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...