በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ጎባ ሪፈራል ሆስፒታል አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አራት ልጆችን በሰላም ተገላግላለች።
ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን በዛሬው ዕለት በሆስፒታሉ በተደረገላት ቀዶ ጥገና 2 ወንድ እና 2 ሴት ልጆችን በሰላም መገላገሏን የዩኒቨርሲቲው መረጃ ያመላክታል፡፡
ወ/ሮ ጠይባ ሀሳን የሀሮ ዱማል ከተማ ነዋሪ ስትሆን÷ከዚህ በፊት ሰባት ልጆች እንዳሏት ተጠቁሟል፡፡
ለአንድ ወር ከ10 ቀን በሆስፒታሉ ውስጥ እንድትቆይ በማድረግ ክትትል ሲደረግላት እንደነበር ተጠቅሷል፡፡
በአሁኑ ሰዓት እናትና የተወለዱት አራቱ ሕጻናት በሆስፒታሉ የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን÷ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙም ተገልጿል፡፡
