አየር መንገዱ 6 ዘመናዊ ድሪም ላይነር አውሮፕላኖችን ሊገዛ ነው

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስድስት ዘመናዊ ቦይንግ 787-9 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን ለመግዛት ከቦይንግ ኩባንያ ጋር ተፈራርሟል።

አየር መንገዱ በአሜሪካ ቨርጂኒያ ከኩባንያው ጋር ያደረገው ግዙፍ ስምምነት የአየር ላይ የበላይነቱን ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል።

የአውሮፕላኖቹ ግዢ ከአዲስ አበባ ወደ አውሮፓ፣ እስያና ሰሜን አሜሪካ የሚደረጉ አህጉር አቋራጭ በረራዎችን ይበልጥ ምቹና ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል።

አውሮፕላኖቹ በነዳጅ ቆጣቢነታቸው እና በጭነት አገልግሎት ውጤታማነታቸው ተመራጭ እንደሆኑም ተገልጿል።

ይህ ግዢ አየር መንገዱ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ያለውን ግዙፍ የድሪምላይነር ስብስብ ይበልጥ የሚያጠናክርለት ይሆናል ተብሏል።

አየር መንገዱ እንዲህ ያሉ ግዙፍ ኢንቨስትመንቶች ውስጥ መግባቱ በ2035 በዓለም ቀዳሚ ከሆኑ 20 አየር መንገዶች ተርታ ለመሰለፍ የያዘውን ግብ እንደሚያፋጥነው ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...