አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

Date:

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል አሉ የተባበሩት መንግስታት እና የአፍሪካ ህብረት መሪዎች።

በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ የገቡት የተባበሩት መንግስታት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ጋር ተወያይተዋል።

ዋና ፀሐፊው በውይይቱ ወቅት፤ የአፍሪካ ህብረትን ድምጽ በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ በማሳደግ ረገድ እየተሰራ ያለውን ስራ አድንቀዋል።

አፍሪካ በባለብዙ ወገን ማሻሻያዎች ላይ ገንቢ ሚና እንዳላት ገልጸዋል።

የተባበሩት መንግስታት እና የአፍሪካ ህብረት ዘርፈ ብዙ ስትራተጂካዊ ትብብር እንዳላቸው ጠቅሰዋል።

የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፤ ዋና ጸሐፊው የአፍሪካ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነትን እንዲጠናከር ላሳዩት ቁርጠኝነት አመስግነዋል።

የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት አጋርነት ሰላምን፣ ደህንነትን እና ዘላቂ ልማትን ለማፋጠን ወሳኝ መሳሪያ መሆኑንም አንስተዋል።

ሁለቱ መሪዎች ከአጀንዳ 2063 እና ከተባበሩት መንግስታት ቻርተር ጋር የተጣጣመ ትብብርን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

መሪዎቹ በቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነት፣ ዘላቂ ልማት፣ ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ሽግግር፣ በኢንዱስትሪ ልማት፣ በስራ ዕድል ፈጠራ እና ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባት ዙሪያ መክረዋል።

የአፍሪካ የልማት ፋይናንስ ፍላጎቶች በበቂ ሁኔታ እንዲፈቱ ፍትሐዊ የፋይናንስ ተደራሽነት፣ የተረጋጋ የዕዳ ሥርዓት እና የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓቶች እንዲሻሻሉ ለማስቻል መስራት እንደሚያስፈልግ ተግባብተዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ማሻሻያ በማድረግ አፍሪካ በምክር ቤቱ ቋሚ ውክልና ሊኖራት እንደሚገባ አጽንዖት ሰጥተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የምርጫ ካርድ፡ የአገር ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ

ግዮን መጽሔት :- በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጉዞ ውስጥ ምርጫዎች የሥልጣን...

አደይ ኢትዮጵያ ጓል አስመራ…!!

የቀድሞ ፕ/ት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የስንብት ቃል ለጠቅላይ ሚ/ር ዐብይ...

ትራምፕ ከኢራን ጋር በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ሁለተኛው ዙር ድርድር ሊደረግ እንደሚችል ተናገሩ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ሁለተኛ ዙር የሰላም ድርድር...

በ”ፊንቴክ” ኢንቨስትመንት በተጠረጠሩት ላይ ተጨማሪ ጊዜ ተፈቀደለት

ፖሊስ ተጨማሪ 14 ቀን ለምርመራ እንዲፈቀድለት ባለፈው አርብ በነበረው...