የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ የሚፈጽመውን ግድያ የሚያወግዝ የውሳኔ ሃሳብ ሐሙስ ዕለት ካጸደቁ በኋላ፣ የአውሮፓ ህግ አውጪዎች ለኢራን ህዝብ ጠንካራ የድጋፍ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ገለጹ።
ሜትሶላ በኤክስ ገጻቸው ላይ “ከአውሮፓ ፓርላማ ለኢራን ህዝብ የተላለፈ ጠንካራ፣ ግልጽና የማይናወጥ መልዕክት፡ እኛ ከእናንተ ጋር ነን” ሲሉ ጽፈዋል።
አክለውም፤ “ዛሬ የአውሮፓ ፓርላማ አባላት የኢራን አገዛዝ የሚፈጽመው አረመኔያዊ ጥቃት በአስቸኳይ እንዲቆምና ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ በከፍተኛ ድምፅ ጠይቀዋል” ብለዋል።
በተጨማሪም ሜትሶላ ከኢስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኃይል ጋር የተያያዙ ማዕቀቦች በተግባር ላይ እንዲውሉ ጥሪ አቅርበዋል።
“በሽብርተኛው የኢስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኃይል አባላት ላይ የተጣለው ማዕቀብ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መሆን አለበት። ምንም ዓይነት ክፍተት ወይም ሰበብ ሊኖር አይገባም” ሲሉ ጽፈዋል።
“ኢራን ነጻ ትወጣለች” ሲሉም አክለዋል፤ ፕሬዚዳንቷ፡፡
