አፍሪካ ውስጥ ሁለት ጂኦ ፓርኮች ብቻ መመዝገባቸው “አሳዛኝ” ነው

Date:

ይህንን እውነታ ለመቀየር ያሰበ ቀጣናዊ መድረክ ዛሬ በአዲስ አበባ ተከፍቷል። የቱሪዝም ሚኒስቴር ከተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ድርጅት ጋር በመተባበር ያሰናዳው ዝግጅት በዘርፉ ኢትዮጵያ የያዘችውን አቅም አጉለቶ ለማሳየት ያለመ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ጂኦ ፓርኮችን ማስመዝገቧ ለምርምር እንደሚጠቅም፣ በዙሪያቸው ያሉ ማሕበረሰቦችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ እና ዓለም አቀፍ እውቅናን እንዲያገኙ እድል እንደሚፈጥር የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ ተናግረዋል፡፡

በዓለም አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ ጂኦ ፓርኮች ቁጥር 229 እንደሆኑም ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ በጂኦ ፓርክነት ልታስመዘግባቸው የሚችሉ ብዙ ቦታዎች እንዳሏት የጠቆሙም ሲሆን ለማሳያነት በጠቀሱት መልካ ቁንጥሬ የመድረኩ ተሳታፊዎች ምልከታ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል፡፡

መልካ ቁንጥሬ መካነ ቅርስን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ለዩኔስኮ ሠነድ መላኩ የሚታወስ ነው፡፡ ቦታው የሰው ልጅ፣ የእንስሳትና የጥንት የሰው ልጅ ሲጠቀምባቸው የነበሩ የድንጋይ መሳሪያዎች እንደሚገኙበት ይነገራል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...