ቴህራን እስራኤል እና አሜሪካ የከፈቱትን ጥቃት ተከትሎ በዓለም ወሳኙ የነዳጅ ዘይት መተላለፊያ በሆነው የሆሙዝ የባሕር ሰርጥን ላይ ለማለፍ በሚሞክሩ መርከቦች ላይ ጥቃት እንደምትፈጽም ዛተች።
አንድ ኢራን ባለሥልጣን በሆሙዝ ሰርጥ “ለማለፍ የሚሞክር ማንኛውም መርከብን በእሳት ነው የምንለኩሰው” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ማስጠንቀቂያውን የሰጡት ባለሥልጣን የኢራን እስላማዊ አብዮት ዘብ ዋና አዛዥ አማካሪ የሆኑት ኢብራሂም ጃባሪ በአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀርበው በተናገሩበት ወቅት ነው።
የሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋቱን ያስጠነቀቁት ባለሥልጣኑ መርከቦች “ወደ ቀጠናው መምጣት የለባቸውም። ከባድ የሆነ ምላሽ ከእኛ ይጠብቃቸዋል” ሲሉ ዝተዋል።
ጃባሪ አሜሪካ “የቀጠናውን የነዳጅ ዘይት ተጠምተዋል” ያሉ ሲሆን ኢራን “በቀጠናው የሚገኙ የነዳጅ ማስተላለፊያ ቧንቧዎችን ታጠቃለች፤ ከቀጠናው ነዳጅ እንዲላክ አትፈቅድም” ብለዋል።
