“ኢራን ሚሳኤሎችን የምታስወነጭፍ ከሆነ ቴህራን ትቃጠላለች” -እስራኤል
እስራኤል የፈጸመችውን ጥቃት ተከትሎ፣ ኢራን አጸፋዊ ሚሳኤሎችን ያስወነጨፈችበት የሁለቱ አገራት ፍጥጫ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል።
*እስራኤል በድጋሚ አርብ ምሽት በፈጸመችው ጥቃት በርካታ ኢላማዎች መምታቷን አስታውቃለች።
*በቴህራን የመኖሪያ ህንጻ ላይ በተፈጸመ ጥቃት 20 ህጻናትን ጨምሮ 60 ሰዎች መሞታቸውን የኢራን መንግሥታዊ ሚዲያ ዘግቧል።
*በኢራን አጸፋዊ የሚሳኤል ጥቃቶች ሦስት ሰዎች ሲገደሉ በርካቶች መቁሰላቸውን ባለስልጣናት ተናግረዋል።
*አሜሪካ ወደ ግጭቱ እንድትገባ ከተደረገች ሁኔታዎች የበለጠ ሊያገረሹ ይችላሉ ተብሏል።
*ኢራን ሚሳኤሎችን የምታስወነጭፍ ከሆነ መዲናዋ “ቴህራን ትቃጠላለች” ሲሉ የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር አስጠንቅዋል።
- የእስራኤል መከላከያ ኃይል ዘጠኝ የኢራን የኒውክሌር ሳይንቲስቶችንና ባለሙያዎችን ገድያለሁ አለ። ጦሩ ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ በፈጸመው ተከታታይ ጥቃት የገደላቸው የኒውክሌር ሳይንቲስቶች ስድስት ናቸው ብሎ ነበር።
*ኢራን በእስራኤል ላይ እየወሰደች ያለችውን አጸፋዊ እርምጃ ለማስቆም አሜሪካ፣ ፈረንሳይና ዩናይትድ ኪንግደም እስራኤልን የሚያግዙ ከሆነ፣ በቀጣናው የሚገኙ የጦር ሰፈሮቻቸውን ኢላማ እንደምታደርግ ማስጠንቀቋን የኢራን መንግሥታዊ ሚዲያ ዘግቧል።
(ቢቢሲ)
