ኢትዮጵያ በህዝብ ትራንስፖርት ዘርፍ ተምሳሌታዊ ለውጥ በማስመዝገብ ተሸለመች

Date:

ኢትዮጵያ የህዝብ ትራንስፖርት ዘርፍ ተምሳሌታዊ ለውጥ በማስመዝገብ ላደረገችው ልዩ ጥረት ዛሬ በኢስዋቲኒ ታላቅ ሽልማት አግኝታለች።

ሽልማቱን የሰጡት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ የመንገድ ደህንነት ልዩ መልዕክተኛ ሚስተር ዣን ቶድት ከኢስዋቲኒ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር በመሆን ነው።

ይህ ሽልማት ኢትዮጵያ ዘላቂ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ቀልጣፋ የህዝብ ማመላለሻ ስርዓቶችን ለማራመድ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል።

እውቅናው በአህጉሪቱ የመንገድ ደህንነት እና የትራንስፖርት ትራንስፎርሜሽን መለኪያዎችን በማስቀመጥ ሀገሪቱ እያደገች ያለችውን ሚና ያሳያል።

በስነስርዓቱ ላይ ኢትዮጵያን ወክለው እየተሳተፋ ሚገኙት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር በረኦ ሀሰን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “በዚህ ስኬት በእውነት ኩራት ይሰማናል፣ በመንገድ ደህንነት ላይ ያለንን ሁለንተናዊ ትኩረት እንድንጠብቅና በዘርፋ ግስጋሴያችንን እንድንቀጥል ያበረታታናል ብለዋል።

https://www.facebook.com/share/p/1EAxTN8E3f

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የምርጫ ካርድ፡ የአገር ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ

ግዮን መጽሔት :- በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጉዞ ውስጥ ምርጫዎች የሥልጣን...

አደይ ኢትዮጵያ ጓል አስመራ…!!

የቀድሞ ፕ/ት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የስንብት ቃል ለጠቅላይ ሚ/ር ዐብይ...

ትራምፕ ከኢራን ጋር በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ሁለተኛው ዙር ድርድር ሊደረግ እንደሚችል ተናገሩ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ሁለተኛ ዙር የሰላም ድርድር...

በ”ፊንቴክ” ኢንቨስትመንት በተጠረጠሩት ላይ ተጨማሪ ጊዜ ተፈቀደለት

ፖሊስ ተጨማሪ 14 ቀን ለምርመራ እንዲፈቀድለት ባለፈው አርብ በነበረው...