ኢትዮ ቴሌኮም እና ሳዑዲ ቴሌኮም የቢዝነስ አጋርነታቸውን ለማጠናከር ተወያዩ

Date:

በሳዑዲ ቴሌኮም የሴልስ ከርየር እና ሆልሴል ምክትል ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ዚያድ ሃማድ ኤ. አልሃሶን እና የከርየር ሴልስ ዳይሬክተር ሚስተር ባንደር ኤ. አልኮዳይር የተመራ ልዑክ ከኢትዮ ቴሌኮም ማኔጅመንት አባላት ጋር ውይይት አካሄዷል፡፡

ውይይቱ በሁለቱ ኦፕሬተሮች መካከል ያለውን አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል የተባለ ሲሆን ነባሩን የቢዝነስ ትብብር ለማሳደግ፣ አዳዲስ የዕድገት አማራጮችን ለመክፈት እና የተለያዩ የዲጂታል አገልግሎቶችን ለማቅረብ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ውይይቱን የመሩት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬሕይወት ታምሩ በወቅቱ “ለጋራ ተጠቃሚነት ብዙ ልንተባበርባቸው እና አዳዲስ የዕድገት አማራጮችን ልንፈልግላቸው የምንችላቸው ዘርፎች አሉ” ያሉ ሲሆን፤  “እነዚህም የአገሮቹን ዲጂታል ሽግግር የሚያሳድጉ እና የዲጂታል ኢኮኖሚ ልማትን የሚያፋጥኑ ዕድሎች ናቸው” ብለዋል።

በውይይቱ ኢትዮ ቴሌኮም እና የሳዑዲ ቴሌኮም ኩባንያ ያላቸውን ሀብት እና የጋራ ትብብር ሆልሴልን እና ከርየርን ለማስፋፋት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል የተባለ ሲሆን በተለይም በፊንቴክ፣ በአለም አቀፍ ሀዋላ፣ በተለያዩ የዲጂታል መፍትሄዎች እና በርካታ የቢዝነስ ዘርፎች ላይ የአዳዲስ እድሎችን በር የሚከፍት ይሆናል ተብሏል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...