ከአውሮፓ አገራት ዘመናዊ አልባሳትን እያስመጣ ለተጠቃሚዎች እያቀረበ የሚገኘው ቪ አይ ፒ ሜንስ ፋሽን የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 24 2017 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ ይከፈታል ተብሏል::
የቪ አይ ፒ ፋሽን ዋና ተልእኮ ሁለት ገጽታዎች አሉት፡ አንደኛ፣ ለኢትዮጵያ ሸማቾች የቅርብ ጊዜ ዓለም አቀፍ የፋሽን አዝማሚያዎችን በተመጣጣኝ እና በተወዳዳሪ ዋጋ ማቅረብ ነው።
ሁለተኛዉ አስፈላጊ የሆነው የኢትዮጵያን የበለፀገ የባህል አልባሳት ቅርስ ከፍ ማድረግ ነው፡፡
ኩባንያው ከታዋቂ ዲዛይነሮች ጋር በመተባበር የሀገራችንን ባህላዊ ልብሶች በዘመናዊ ዲዛይኖች በማስተዋወቅ በአለም አቀፍ ገበያ ተፈላጊ እና ተመራጭ እንዲሆኑ በማድረግ የኢትዮጵያን ፋሽን ለዓለም ለማስተዋወቅ እየሰራ ይገኛል፡፡
ቪ አይ ፒ ሜንስ ፋሽን በቦሌ ብራስ ሪያሊቲ ፕላዛ ህንፃ ምድር ላይ በከፈተው የመሸጫ ሱቅ በዕለቱ ከሌሎች ኢቨንት አዘጋጆች ጋር በመሆን የፋሽን ሾው ትርኢት ማዘጋጀቱም ተሰምቷል::
ነሐሴ 24/ 2017 ዓ.ም በሚካሄደው የፋሽን ትርኢቱ ላይ ደረጃቸውን የጠበቁ አልባሳት በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለያዩ አገራት ላይ መለበስ እንዲችሉ እና የሀገራችንን ምርቶች በዓለም ላይ እንዲተዋወቁ ለማድረግ መታቀዱ ተነግሯል::
የኢትዮጵያን ፋሽን ስለማስተዋወቅ፡ “የእኛ ቅርስ በማይታመን ሁኔታ የበለፀገ ነው።
የእኛ ራዕይ ከኢትዮጵያ ብሩህ ዲዛይነሮች ጋር በመተባበር ባህላዊ ልብሶችን ለአለም አቀፍ ታዳሚዎች እንደገና መፍጠር ነው፡፡
የእኛ ዘመናዊ ‘ሀበሻ’ ዲዛይኖች የብሔራዊ ኩራት እና ለዓለም አቀፍ ፋሽን ኢንዱስትሪ ትልቅ የወጪ ንግድ ሊሆኑ እንደሚችሉ እናምናለን”ሲሉ የድርጅቱ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ ተናግረዋል ።
አድራሻችን :-አዲሱና ሰፊው ማሳያ ክፍል ቦሌ ዩጎ ቸርች አቅራቢያ በሚገኝዉ ያሊት ፕላዛ ግራውንድ ፍሎር ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡
email- vipmensfashion3@gmail.com
adh: +251 960 279 262
