ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞቹ ቁጥር ከ90 ሚሊየን በላይ ደረሰ

Date:

የኢትዮ ቴሌኮም የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፣ ኢትዮ ቴሌኮም በገጠርና በከተማ ባከናወነው የኔትወርክ ማስፋፋት ስራ የደንበኞቹ ቁጥር 90 ነጥብ 1 ሚሊየን መድረሱን አስታውቀዋል። የደንበኞቹ ቁጥር ከባለፈው ዓመት ሲነጻጸር በ8 ነጥብ 3 በመቶ ማደጉን አንስተዋል።

በሌላ በኩል ኢትዮ ቴሌኮም በ2018 በጀት ዓመት 215 ነጥብ 82 ቢሊዮን ብር ገቢ በማግኘት ዓመታዊ ዕቅዱን 99 ነጥብ 7 በመቶ ማሳካቱን ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ገልጸዋል።

የኩባንያው ይኸው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ33 ነጥብ 2 በመቶ የላቀ ዕድገት የተመዘገበበት ነው።

ለተመዘገበው ገቢ ከፍተኛውን ድርሻ ካበረከቱ የአገልግሎት ዓይነቶች መካከል ዋናዎቹ የዳታ እና ኢንተርኔት አገልግሎት 31 ነጥብ 1 በመቶ፣ የሞባይል ድምጽ አገልግሎት 23 ነጥብ 5 በመቶ ድርሻ ይዟል።

ማሕበራዊ ሃላፊነትን ከመወጣት አንጻር፣ በትምሕርት፣ ጤና እና ሰብዓዊ ድጋፍ ዘርፎች ኢትዮ ቴሌኮም ከ492 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን፣ በስነ ምሕዳሩ ውስጥ ለሚንቀሳቀሱ ከ2 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የስራና የገቢ ዕድል ፈጥሯል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...